Strategic Direction NSPTC Tree Planting Program

NSPTC Tree Planting Program

18th July, 2026

የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ''ተስፋን እንትከል ''በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አካሄደ፡፡
09/11/2018 ዓ/ም
የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች፤አሰለልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች አረንጓዴ ልማትን በማጠናከር የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም ለቀጣይ ትውልድ ንፁህና ምቹ አከባቢን ለማስረከብ በሚል ህሳቤ በዛሬው እለት የችግኝ ተከላ መረሀ ግብር ተካሂዷል፡፡
የኮሌጁ ዲን አቶ ሸለማ ንጉሴ በመረሀ ግብሩ ላይ በመገኘት ባደረጉት ንግግር ላይ በዛሬው እለት በኮሌጃችን ማህበረሰብ የተተከሉ የተለያዩ ችግኞች የኮሌጁን አከባቢ አረንጓዴና ውብ ለማድረግ እንዲሁም ለአከባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅእኖ ቅነሳ የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑንና መትከል ብቻ ሳይሆን እነዚህን ችግኞች በመንከባከብ ማፅደቅ ይኖርብናል ብለዋል፡፡
አክለውም አቶ ሸለማ የኮሌጁ ችግኝ ተከላ በዚህ የሚያበቃ ሳይሆን በግቢው ውስጥ አከባቢውን የሚጠብቁና አረንጓዴ ልማትን የሚያጎለብቱ ተግባራትን በቀጣይነት በመተግበር ለሀገራዊ የአረንጓዴ ልማት ግብ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማበርከቱን ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የመርሀ ግብሩ ተሳታፊ ሰራተኞች እንደገለፁት የችግኝ ተከላው የአከባቢ ጥበቃን ከማጠናከር ባሻገር በተቋሙ ውስጥ የመተባበርና የተጠያቂነት ባህልን ለማጎልበት ጭምር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ስላለዉ እኛም መትከል ብቻ በቂ ነው ሳንል በእንክብካቤው ላይም በትኩረት ልንሳተፍበት ይገባል ብለዋል ፡፡

.

Copyright © All rights reserved.

Created with