Strategic Direction Nsptc Colidor Development

Nsptc Colidor Development

18th July, 2026

የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ልህቀትን ከሀገራዊ የልማት ግቦች ጋር በማጣመር ግቢውን ለስልጠና፣ ለቴክኖሎጂ ፈጠራና ለቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥ ምቹ፣ ጽዱ እና ውብ የማድረግ ታላቅ ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል
ኮሌጁ ለሰልጣኞች ፣ ለሰራተኞች ና ለማህበረሰቡ ምቹ ና ሳቢ የስራና የስልጠና የአካባቢን በመፍጠር ስነ-ልቦናዊ ዝግጁነትን እና የበቃ የሰው ሃይል ምርታማነትን ለማሳደግ በከፍተኛ ሁኔታ እያሰራ ነው።
ኮሌጁ የቴክኒክና ሙያ ልህቀትን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን፣ የስራ እና የስልጠና አከባቢን ምቹ ና አግልግሎትን ለማሻሻል የተጠቃሚዎችን ስነ-ልቦናዊ ዝግጁነት እና ምርታማነት ለማሳደግ ያለውን ሚና በመገንዘብ ለዚህ ተግባር ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
ዋና ዋና ትኩረቶች
• የአረንጓዴ ስነ-ምህዳር ግንባታ፦ በግቢው ውስጥ የሚገኙ ክፍት ቦታዎችን በተመረጡ እፅዋት፣ ለምለም ሳሮች እና ውብ አበባዎች የመሸፈን ስራ።
• የማረፊያ እና የፅሞና ስፍራዎች ማዘጋጀት፦ ለሰልጣኞች ከስልጠና ሰዓት ውጭ በነፃነት የሚያጠኑባቸው እና የሚያርፉባቸው ምቹ የንባብ ማዕዘናት መፍጠር።
• የፅዳት እና የስነ-ስርዓት ባህል፦ አጠቃላይ የኮሌጁን ግቢ ውበት ዘላቂ ለማድረግ የአካባቢ ጥበቃ እና የፅዳት አጠባበቅን ከኮሌጁ እሴቶች ጋር የማዋሃድ ስራ።
የተቋም ውበት የማንነታችን መገለጫ ብቻ ሳይሆን፣ የቴክኖሎጂ፣ የሃሳብ ፈጠራ እና ጥራት ያለው ስልጠና መሰረት ነው"
የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ሸለማ ንጉሱ እንደገለጹት፤ ኮሌጁን በሀገርና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ ስታንዳርዱን የማስጠበቅ፣ የመዘመንና በሁሉም ረገድ የላቀ ውጤት የማስመዝገብ ስራው በቁርጠኝነት ይሰራል ብሏል።
በተጨማሪም ኮሌጃችን ራሱን በማደስና የላቀ የስልጠና አከባቢን በመፍጠር የለውጥ ግንባር ቀደም ምሰሶ መሆኑን ይቀጥላል ብሏል።
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

     

.

Copyright © All rights reserved.

Created with